/ከኦሮሞኛ የተተረጎመ/
በአንድ በህግ የምትተዳደር ሀገር ዉስጥ ሁለት መንግስት አብሮ ሊኖር አይችልም::መንግስት እና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በሰላም ተከባብረዉ ድርሻቸዉን አዉቀዉ በሰላም እና በህግ አግባብ ተፎካክረዉ አብሮ መኖር ያለነዉ ዘመናዊነትም ነዉ::የህግ የበላይነትን የማስከበር: የጦር መሳርያ መያዝ እና መምራት የመንግስት ሀላፊነት እና ድርሻ መሆኑን ሊሰመርበትና ሊታወቅ ይገባል::(Only as a monopoly as means of violence)የፖለታካ ድርጅቶች የመንግስት ስልጣን ለመያዝ በሰላማዊ መንገድ መታገል ትጥቃቸዉ ሀሳብ ነዉ ! ትጥቃቸዉ የፖለቲካ ፕሮግራማቸዉና ደጋፊዎቻቸዉ ናቸዉ::
ከዚህ ዉጪ በየትኛዉም ሀገር ዉስጥ አንድ የፖለቲካ ተፎካካሪ ፓርቲ በአንድ በኩል በሰላማዊ ትግል በሌላ ጎን ደግሞ መሳርያ ታጥቆ መንቀሳቀስ በጭራሽ የሚቻል አይደለም::በየትኛዉም ሀገር ሆኖም አያዉቅም::ኦሮሞ መሳርያ መታጠቅ ማለት እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ከትጥቅ ትግል ወደ ሰላማዊ ትግል የተጋበዘ አካል ትጥቅ መፍታት የለበትም የሚል ጉዳይ የሚገናኝ አይደለም ::ስለሆነም ይህ ሁለት ጉዳይ አብሮ ማምታታት ተቀባይነት የለዉም ::