46ኛው የካራማራ ድል በአዲስ አበባ ተከበረ

46ኛው የካራማራ ድል በአዲስ አበባ ተከበረ

ኢትዮጵያ በወራሪው የሶማሊያው የሲያድ ባሬ መንግሥት የተቃጣባትን ጥቃት የመከተችበት የካራማራ ድል 46ኛው ዓመት የድል በዓል ዛሬ የካቲት 26ቀን2016 በድላችን ሐውልት ( ኢትዮ ኩባ የወዳጅነት አደባባይ) ውስጥ ተከብሯል።

በዚህ ሥነ ሥርዓት ላይ በወቅቱ በጦርነቱ ላይ ጉልህ የጦር ጀብዱ የፈፀሙ ጀኔራል መኮንኖች ተገኝተዋል ። በበዓሉ ላይ በጦርነቱ ወቅት ከኢትዮጵያ ጎን ተሰልፈው የተዋጉ ኩባውያንና በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደርም በመታስብያ ስነስርአቱ ላይ ተገኝተዋል ።

አያሌ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም የታደሙበት ይህው የካራማራ ድል መታሰቢያ ስነስርአት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ  በየዓመቱ በድምቀት በመከበር ላይ ነው።

LEAVE A REPLY