ኢትዮጵያ የመተንፈሻ ቀዳዳ የተሠራላቸው ማስኮችን ወደ ሀገር እንዳይገቡ አገደች

ኢትዮጵያ የመተንፈሻ ቀዳዳ የተሠራላቸው ማስኮችን ወደ ሀገር እንዳይገቡ አገደች

ኢትዮጵያ ነገ ዜና– የኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን “ራስ ወዳድ” የሚል መጠሪያ የተሰጣቸው፣ ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተሠራላቸው ማስኮችን ወደ ሀገር እንዳይገቡ ማገዱ ተሰማ።

ባለሥጣኑ ከቀናት በፊት ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተገጠመላቸው ማስኮች የቫይረሱን ሥርጭት ለመጨመር አስተዋፅዖ  ስላላቸው ኅብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ምክር ለግሶ ነበር።
ይሁን እንጂ  ህብረተሰቡ እነዚህን ማስኮች ከመጠቀም አለመቆጠቡን ተከትሎ ተቋሙ ዳግም ማስተንፈሻ ያላቸው ማስኮች ወደ ሀገር ቤት እንዳይገቡ ትዕዛዝ ለመስጠት ተገዷል ነው የተባለው።
በባለሥልጠኑ የመድኃኒት ምዝገበ እና ፍቃድ ዳይሬክተር  አቶ አብደላ ጣሰው፤ እነዚህ ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተገጠመላቸው ማስኮችን፣ ቫይረሱን ለመከላከል በሚል ዓላማ እናስገባ ለሚሉ ሰዎችም ሆነ ሀገር ውስጥ ለማምረት  ፍቃድ ለሚጠይቁ ሰዎች ፈቃድ መስጠት እንደቆመ አረጋግጠዋል።
በተለይ  ቫይረሱን ለመከላል በሚል ዓላማ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡም ለጉምሩክ ኮሚሽን ደብዳቤ መጻፉን የተናገሩት ሓላፊው፤ እነዚህ ማስኮች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ሲደረግ የተሠሩበት ዓላማ በሽታውን ለመከላከል በሚል ባለመሆኑ፣ እንዲሁም ማስኮቹ በተገጠመላቸው የመተንፈሻ ቀዳዳ አማካኝነት ቫይረሱን ከመከላከል ይልቅ ለስርጭቱ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ስለሚኖራቸው ሕዝብ  ማስኩን ከመጠቀም ሊቆጠብ ይገባል ብለዋል።

LEAVE A REPLY