ኢትዮጵያ ነገ ዜና፡– በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዐታት በተደረገ 10ሺኅ 919 የላብራቶሪ ምርመራ፣ 801 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስትር አስታወቀ።
በተጠቀሰው ሰዐታት ውስጥም የ10 ሰዎች ሕይወት አልፏል። ይህም አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 390 አድርሶታል።
በአንጻሩ ትናንት 292 ሰዎች ማገገማቸውን ተከትሎ እስካሁን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 9 ሺኅጨ707 የደረሰ ሲሆን፤ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 22 ሺኅ 253 መድረሱ ታውቋል።

























