በነቀምት ህዝባዊ ተቃውሞ ተነስቷል

በነቀምት ህዝባዊ ተቃውሞ ተነስቷል

/ኢትዮጵያ ነገ ዜና/፡ – በነቀምት ከተማ ዛሬ በተቀሰቀስው ህዝባዊ ተቃውሞ በርካታ ሰዎች አደባባይ በመውጣት አገዛዙ በተለይ በህዝብ ላይ የጣለው ስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲነሳ ሲጠይቁ ውለዋል፡፡

በከተማው የተሰማሩ ውታደሮች እንዲነሱ የጠየቁት ስልፈኞች የተለያዩ መፈክሮችን ሲያሰሙ ተስተውለዋል፡፡ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፉን ለመበተን በአካባቢው የተሰማሩ የመንግስቱ ወታደሮች ጥይቶችን ሲተኩሱ ተስተውሏ፡፡

አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በብዙ የፖለቲካ ተንታኞችና አለም አቀፍ ተቋማት ሲወገዝ የሰነበተ ሲሆን ከእስር የተፈቱ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ መሪዎችም ህዝብን ለተቃውሞ የሚቀሰቅስ መሆኑን በማስመር በአስቸኳይ እንዲነሳ ሲወተውቱ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም፡፡

LEAVE A REPLY