ሞተች የተባለችው ለሠርግ እየተዘጋጀች ነው! || አብርሃ በላይ

ሞተች የተባለችው ለሠርግ እየተዘጋጀች ነው! || አብርሃ በላይ

ሰዎች ሙታለች ካልዋት ሁለት አመት ሁኗታል። እስዋ ግን ጭራሽ ለሠርግ እየተዘጋጀች ነው። የፖለቲካ ሠርግ! ትህነግ አገር-አቀፍ ጉባኤ በመቀሌ ለማዘጋጀት የልጅዋ ሠርግ እንዳማረላት ባልቴት ከአዳራሽ ወደ ኩሽና፣ ከኩሽና ወደ አዳራሽ ተፍ ተፍ እያለች ትገኛለች። እንደ አብርሃ ደስታ ዘገባ ከሆነ፣ ትህነግ 47 የፖለቲካ ድርጅቶችን ጋብዛለች። (ድርጅቶቹ እሷ ጋር ሲሆኑ እንዳሸን ይበዛሉ!)። እያንዳንዱ ድርጅት ደግሞ አምስት እንግዶችን ይዞ መቀሌ ከች አንዲል የአየር ትኬት ተቆርጦለታል።

ትህነግ በሰርጓ ሰሞን ልዩ ደስተኛ እንድትሆን ያረጋት ጉዳይ ደግሞ አንድ ሰው ነው – ለማ መገርሳ! ለማ ትህነግን ታግሎ ወደ መቀሌ እንድታፈገፍግ ካደረጉት አንዱ ቢሆንም፣ ከትህነግ ጋር ግን እንደ አሸባሪው የቄሮ ጌታ ጃዋር መሐመድ የስትራተጂ አጋር (strategic partner) ነው። ሁሉም አገር-አፍራሹን የዘር ፌዴራሊዝሙን እስከመጨረሻ የደም ጠብታ እንጠብቀዋለን ባይ ናቸው። ያ የመቀሌ ጉባኤ ለዳግማይ ኢህአዴግ ትንሳኤ ዘሙታን ይሁን ለሽግግር መንግስት ቻርተር ዝግጅት የታወቀ ነገር የለም።

ለማንኛውም የነሱ ነገር እስኪለይለት ድረስ፣ በኛ በኢትዮጵያውያን አንድነት ኃይሎች በኩል እንደንጋት ኮከብ ቦግ ብሎ መብራት የጀመረውን አንድ ለናቱ ባልደራስን ኢትዮጵያችንን ሊታደግ የተፈጠረ ህዝባዊ ኃይል ያድርግልን!

LEAVE A REPLY