የኮሮናን መድኃኒት በአፍሪካ ለማግኘት ድጋፍ የሚያደርግ ኮሚቴ በዓለም ጤና ድርጅት ተቋቋመ

የኮሮናን መድኃኒት በአፍሪካ ለማግኘት ድጋፍ የሚያደርግ ኮሚቴ በዓለም ጤና ድርጅት ተቋቋመ

A coronavirus diagnostic test kit sits displayed in this arranged photo at the TIB Molbiol Syntheselabor GmbH production facility in Berlin, Germany, on Thursday, March 6, 2020. TIB has reoriented its business toward coronavirus, running its machines through the night and on weekends to make the kits, which sell for about ???160 ($180) apiece. Photographer: Krisztian Bocsi/Bloomberg

ኢትዮጵያ ነገ ዜና || ለገዳዮ ኮሮና ቫይረስ የሚሆን መድኃኒትን ከባሕላዊ መድኃኒቶች ለማግኘት የሚደረግ ጥረትን የሚደግፍ፣ የሚያማክር ኮሚቴ በዓለም ጤና ድርጅት እና በአፍሪካ የበሽታ መከላከያ ማዕከል አማካይነት መቋቋሙ ተሰማ።

በኮሚቴው ውስጥ የሚሳተፉት ባለሙያዎች የአፍሪካ አገራት ባሏቸው ባሕላዊ መድኃኒቶች ዙሪያ በሳይንስ፣ ደኅንነታቸውን የተጠበቀ በማድረግና በጥራት በኩል እንደሚያማክሩ ተነግሯል።
በአማራጭነት ባሕላዊ መድኃኒቶችን ለኮሮና ቫይረስ ለማዋል የሚደረገውን ጥረትን የሚደግፈው ኮሚቴ፤ ሀገራት በመድኃኒቶቹ ላይ በሚያደርጉት ሙከራ ወቅት አስፈላጊውን ዓለም ዐቀፋዊ የጥራት ደረጃዎችን የጠበቁ እንዲሆኑ ድጋፍ እንደሚያደርግ ከዓለም ጤና ድርጅት የወጣው ማብራሪያ ያመላክታል።
ዓለም ለኮሮና ቫይረስ የሚሆን የመከላከያ ክትባት እና የፈውስ መድኃኒት ለማግኘት በምትጥርበት ወቅት፤ በባሕላዊ ሕክምናው ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ለመጠቀም የሚደረገው ጥረት ሳይንስን መሰረት ያደረገ መሆን እንደሚገባው የአፍሪካ አካባቢ የዓለም ጤና ድርጅት ሓላፊ ማሲዲሶ ሞይቲ አስታውቀዋል።
ይህ የባለሙያዎች ኮሚቴ የተመሠረተው ከተለያዩ እጸዋት የተዘጋጀውን “የኮቪድ-19 መድኃኒት ነው” በማለት በስፋት ስታስተዋውቅ የነበረችው ማዳጋስካር በበሽታው የተያዙ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሕሙማን በሀገሯ ከመገኘቱ ጋር በተያያዘ እንደሆነ ተነግሯል።
ማዳጋስካር  ውስጥ ተገኘ በተባለው የኮሮና ቫይረስ መድኃኒት ላይ፤  ፍተሻ  ያደረጉት የናይጄሪያ ተመራማሪዎች በትክክለኛው መንገድ ወረርሽኙን የመፈወስ ይዘት ማግኘት እንዳልቻሉ ከጥቂት ቀናት በፊት መግለጻቸው ይታወሳል።
የማዳጋስካሩ ፕሬዝዳንት ሳይቀሩ ስለመድኃኒቱ ፈዋሽነት በመገናኛ ብዙኃን ላይ ቀርበው ተደጋጋሚ ማብራሪያ የሰጡ ቢሆንም፤ ጥቂት የማይባሉ የሀገሪቱ ምክር ቤት እንደራሴዎች በበሽታው መያዛቸውና ሁለቱ  መሞታቸው የመድኃኒቱን ፈዋሽነት አጠራጣሪ አድርጎታል።
ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ  ወረርሽኙ በሕዝቡ ውስጥ ተዛምቶ፣ በየዕለቱ በርካታ ማዳጋስካራዊያን በበሽታው መያዛቸው ከመሰማቱ ባሻገር  የሕክምና ተቋማት እየጨመረ በሚሄድ ከአቅማቸው በላይ በሆነ የህሙማን ቁጥር መጨናነቃቸው ታውቋል።

LEAVE A REPLY